እንኳን ለዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ለምኵራብ) በሰላም አደረሳችሁ!
እንኳን ለዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ለምኵራብ) በሰላም አደረሳችሁ!
“ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ትሰመይ”(“ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላላች” ማቴ.21÷13)
ምኵራብ ማለት:- የአይሁድ መሰብሰቢያ አዳራሽ ፣ ቤተ መቅደስ ፣ ኮረፍታ ማለት ነው
በዚህ ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቤተ መቅደሱን ክብር የገለጠበት በአንጻሩ ለቤተ መቅደሱ ክብር ሳይሰጡ በቤተ መቅደሱ የማይገባ ስራ የሚሰሩትን የገሠጸበትና ያስተማረበት ነው።
ቤተ መቅደስ የተባለው የኢያንዳንዳችን ልብ ነውና ልባችነን አንጽተን የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ እንዲሆን የሚያስተምር ነው።
የምኵራብ ዕለተ እሑድ የካቲት ፳፪ ( 22 ) ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ (2018) ዓ. ም (March 1/2026) ከደረሱት የስብሐት ነግህ፣ የኪዳን፣ የቅዳሴ፣ የስብከተ ወንጌልና የዝማሬ አግልግሎት መካከል በጥቂቱ፦

በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት የደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ስታቫንጋር፣ ኖርዌይ
