እንኳን ለዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት (ኒቆዲሞስ) በሰላም አደረሳችሁ!

የአይሁድ አለቃ፣ የእስራኤል መምህር ኒቆዲሞስ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃለ ምልልስ ካስተማራቸው ጥቂት ዕድለኛ ሰዎች አንዱ ነው፡፡ «ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ ስለ መወለድ» ዮሐ. ፫፥፮ ጌታችን ኒቆዲሞስን በምሳሌ አድርጎ ያስተማረው ሲሆን ሌሊት ከአምላኩ ተምሮ ምሥጢሩ የተገለጸለት ኒቆዲሞስ ቀድሞ በአደባባይ ሄዶ መማርን ቢፈራም ምሥጢሩ ሲገለጽለት ግን አይሁድ ጌታችንን በሰቀሉት ዕለት ፍርኃት ርቆለት ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ቅዱስ ሥጋውን ገንዞ ለመቅበርም በቅቷል፡፡ ለኒቆዲሞስ ምሥጢሩን እንደ ገለጸ ለእኛም ይግለጽልን፤ አሜን፡፡
የኒቆዲሞስ ዕለተ እሑድ መጋቢት ፳ ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ ዓ. ም (March 29/2026) ከደረሱት የስብሐተ ነግህ፣ የኪዳን፣ የቅዳሴ፣ የስብከተ ወንጌልና የዝማሬ አግልግሎት መካከል በጥቂቱ፦
በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት
የደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን

ስታቫንጋር ኖርዌይ