ገብርኤል ነው

ገብርኤል አምለክ የሾመዉ

ገብርኤል ነው አምለክ የሾመዉ [2]

አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ከእሳት ያዳነዉ

 

ናቡከደነጾር አንተን በግልፅ አይቶ

ለእግዚአብሄር ሰገደ ያንተን ምስል ትቶ

ሐሰቴን እንደሆነ ይመስክሩ ሶስቱ

ከዚያች ከባቢሎን [2] የወጡት ከእሳቱ

አዝ..

 

ከዓለመ መላእክት ከቅዱሱ ቦታ

የሰዉን ልጅ መረጥህ ልትረዳ ጧት ማታ

እንደ ጌቤናይቱ ቅድስት እየሉጣ

ትመስክር ስለአንተ [2] ከነ ልጇ ትምጣ

 

አዝ..

 

ልመስክር ስለአንተ ነህ እና ህይወቴ

ገብርኤል [2] ሰመረ ስእለቴ

የአናብስትን አፍ የዘጋኸዉ መልአክ

ገብርኤል አንተ ነህ [2] በእኛ ሁሉ የታመንክ

 

አዝ..