• ”እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። ” መዝ 135፤ 1

  • ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ!

  • "ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም" ምሳ 22፤6

Medhanealem

እንኳን ለዘመነ ቅበላ(ዘመነ መርዓዊ ወመርዓት) በሰላም አደረሳችሁ!

እንኳን ለዘመነ ቅበላ(ዘመነ መርዓዊ ወመርዓት) በሰላም አደረሳችሁ!
ከነነዌ ፋሲካ ሐሙስ ጀምሮ እስከ ዘወረደ ዋይዜማ ቅዳሜ ድረስ ያለው ዘመን ዘመነ ቅበላ (ዘመነ መርዓዊ ወመርዓት) ይባላል።

እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!

እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!
ጾመ ነነዌ ከሰባቱ የህግ(የቀኖና) አጽዋማት አንዷ ናት ከጥር17 ቀን እስከ የካቲት 21 ቀን ድረስ ባሉት 35 ቀናት ውስጥ ብቻ ትውላለች ከታች ጥር 16 ቀንን ከላይ የካቲት 22 ቀንን አትነካም ዘንድሮ በ2018 ዓ.ም ከጥር 25 እስከ ጥር 27 ቀን ድረስ ትውላች።

አስተርእዮ ማርያም

አስተርእዮ ማርያም

ጥር ፳፩ ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው። እመ ብዙኃን ቅድስት ድንግል

እንኳን ለዘመነ አስተርእዮ በሰላም አደረሳችሁ!

እንኳን ለዘመነ አስተርእዮ በሰላም አደረሳችሁ!
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ መሠረት ከጥር ፲፩(11) እስከ ድኅራረ ጾም ቅዳሜ ደረስ ያለው ዘመን ዘመነ አስተርእዮ ይባላል።( ዘመነ አስተርእዮ ሲበዛ ፶፫(53) ቀን ይሆናል ከጥር ፲፩ (11) እስከ መጋቢት ፫(3) ድረስ ማለት ነው ፤ ሲያጥር ፲፱(19) ቀን ይሆናል ከጥር ፲፩(11) እስከ ጥር ፳፱(29) ቀን ድረስ ማለት ነው።ከእነዚህ ቀናት መካከል አይወጣም።

የ፳፻፲፰ በዓለ ጥምቀት በሀገረ ኖርዌይ ክርስትያንሳንድ

“አሜሃ መጽአ ኢየሱስ እምገሊላ ውስተ ዮርዳኖስ ኀበ ዮሐንስ ከመ ይጠመቅ እምኔሁ” ማቴ 3:13 (“ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ”)

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ!

በመላው ዓለም፣ በሀገራችን ኢትዮጵያ፣ በኖርዲክና ካሪክ ሀገረ ስብከት፣ በኖርዌይ እንዲሁም በስታቫንገር ደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም አብቢያ የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ፦ አባቶች፣ እናቶች፣ ወንድሞች፣ እህቶችና ሕፃናት እንኳን
​ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል (ለብርሃነ ጥምቀቱ) በሰላም አደረሳችሁ!

የ2018 ዓ/ም የእንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳቸሁ መልእክት፣ ከመምህር አብርሃም ሙጭየ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን!
በመላው ዓለም የምትገኙ ፤ በሀገራችን ኢትዮጵያ የምትገኙ ፤ በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ስር የምትገኙ ፤ በሀገረ ኖርዌይ የምትገኙ ፤ እንዲሁም በደብራችን በስታቫንገር ደብረ ገነት መደኃኔ ዓለም አጥቢያ የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕደ እምነት ተከተዮች በሙሉ አባቶች እናቶች ወንድሞችና እህቶች ህፃናትም እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳቸሁ!!!

የመድኃኔ ዓለም ክብረ በዓል ከጥቅም 29 -30/2018 ዓ.ም(November 08-09/2025)

የአባታችንና የአምላካችን የቸሩ መድኃኔ ዓለም ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ ከጥቅም 29 -30/2018 ዓ.ም(November 08-09/2025)  ድረስ  የተከበረው የጥቅምት መድኃኔ ዓለም አመታዊ ክብረ በአል።

የ2018/2025 የመስቅል ደመራ በዓል አከባበር በደብረ ገነት መድኃኔዓለም ወኪዳነምህረት ቤተክርስትያን በስታቫንገር ኖርዌይ

የ2018/2025 የመስቅል ደመራ በዓል አከባበር በደብረ ገነት መድኃኔዓለም ወኪዳነምህረት ቤተክርስትያን በስታቫንገር ኖርዌይ

የመስቀል ደመራ በዓል 2018

የደመራ በዓልን ዓርብ መስከረም16/2018 ዓ.ም(September 26/2025) እስከዛሬ ስናከብርበት በነበረው ቦታ ከ17:00 ሰዓት ጀምሮ እናከብራለን ቀደማችሁ በመገኘት የሥርዓቱና የጸሎቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ

አገልጋዮች

የቤተክርስቲያኑ አመሰራረት ታሪክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ክርስቲያን የተባሉ ምእመናን በኅብረት የሚጠሩበት በመጽሐፍ ቅዱስ ጎልቶ የሚታይ የምእመናን ስያሜ ነው። ማቴ 16፥18  ሐዋ 5፥11፤ 20፥28 ኤፌ 5፥23-33።

ሥርዓተ አምልኮ የተጀመረው እግዚአብሔር ፍጥረቱን እመ ኁበ አልቦ ኁበ ቦ አምጥቶ ከፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ነው። መላእክት ከተፈጠሩበት ጊዜ ጀምሮ ”ቅዱስ፣ቅዱስ፣ቅዱስ” እያሉ ፈጣሪያቸውን በማመስገን አምልኮአቸውን የሚገልጹ ስለሆነ አምልኮተ እግዚአብሔር በዓለመ መላእክት ተጀመረ ማለት ነው /ኩፋ 2፥6 8።

ሰውም በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ለፈጣሪው ይገዛ ነበር። ልጆችም ከአባታቸው ባገኙት መንፈሳዊ ጥበብ መሠረት የአምልኮአቸው መገለጫ የሆነ መሥዋዕት የወንጌል አምሳልና መርገፍ በሆነችው ኦሪት አቅርበዋል።አማናዊት ቤተክርስቲያን የተመሠረተችው ግንቦት 18 ቀን 33 ዓ.ም እንደሆነ ተጽፏል።

በክርስቶስ ደም የተመሠረተችው አንዲት፣ቅድስት፣ኩላዊት፣ሐዋርያዊት ቤ/ያናችን  በአሁኑ ሰዓት በመላው ዓለም ማለትም በአፍሪካ በአሜሪካ፣በካናዳ፣ኢንግላንድን ጨምሮ በመላው አውሮፓ፣ በእስያ ና በኢየሩሳሌም  የምትታወቅ እና ተቀባይነት ያላት ሲሆን ፤ በዚህ በውጭው ዓለም ለሚገኘው ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ እና ለሌላውም ፣ማኅበረሰብ  በስደት ምክንያት ባህሉ ን፣ታሪኲንና ማንነቱን እንዳይረሳ ፣ከሃይማኖቱ እንዳወጣ ለማድለግ ፦ ጳጳሳትን ፣ካህናትን ፣ዲያቆናትን ና መምህራንን ልካ ፦ ሃይማኖታዊ፣ማኅበራዊ፣መንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ሐዋርያዊ  ተልዕኮዋን በመወጣት ላይ ትገኛለች።

በዚሁ መሠርት በኖርዌይ ስታቫንገር  የኢ/ኦ/ተ/  ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ወኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ታላቁ አባት ብጹዕ አቡነ ጎርጎሪዎስ ካልዕ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክንን በዓለም መድረክ ወክለው ከላይ ለተገለጸዉ  ሐዋርያዊ  አገልግሎታቸው ወደ ኖርዌይ ስታቫንገር መምጣታቸውን ተከትሎ እ. ኤ. አ 1994 ዓ.ም በፈቃደ እግዚአብሔር  ልትመሠረት ችላለች ።

ብጹዕ አቡነ ጎርጎሪዎስ ካልዕ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክንን  ታላቅነትና ማንነት በዓለም ያሳወቁ የቤ/ክ ልዩ መልዕክተኛ ነበሩ። ብጹዕ አባታችን ከአምስት በላይ የተለያዩ ቋንቋዎች ተሰጥኦና ልዩ ልዩ የንግግር ጸጋ፣ ሰብኮ የማሳመንና ተናግሮ የማሳሰብ ሃብት ስለነበራቸው ቅዱስ ሲኖዶስ በየጊዜው በተለያዩ ዓለም አቀፋዊ ጉባኤዎች የኢትዮጵያን ቤ/ክ ወክለው እንዲገኙ በወሰነው መሰረት፦ በተለያዩ የዓለም ሀገራት በተካሄዱ ስብሰባዎች ለይ ተገኝተዋል።በዚህም መሠረት በአውሮፓ በነበራቸው አገልግሎት በኖርዌይ ስታቫንገር  ከተማ ይኖሩ ከነበሩት በጣት ከሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ ምእመናን መካከል ወ/ሮ ኂሩት ከበደ እና ቤተሰቦቻቸውን አግኝተው አስተምረው፣ መክረውና አባታዊ ቡራኬ ከሰጧቸው በኃላ ቤተክርስቲያን እንዲመሠርቱ በሰጧቸው አባታዊ ማሳሰቢያ መሠረት ምእመናኑን በማሰባሰብ አገልግሎት  በ20.07.1994 ዓ.ም (እ. ኤ. አ) ተጀመረ።
በ06.04.2005 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ቤተክርስቲኗ በኖርዌይ ሀገር ሕጋዊ ሆና ተመዘገበች።በአሁኑ ሰዓት የምእመናን ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ለማነጽ ወይም ለመግዛት ምእመናን በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ።

አድራሻችን

  • +47 458 50 622
  • Skippergata 67, 4327 SANDNES
  • Postboks 113 Sentrum 4001 Stavanger, Norway

መልዕክትዎትን ያጋሩን