መልአከ ገነት መምህር አብርሃም ሙጭዬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ክርስቲያን የተባሉ ምእመናን በኅብረት የሚጠሩበት በመጽሐፍ ቅዱስ ጎልቶ የሚታይ የምእመናን ስያሜ ነው። ማቴ 16፥18 ሐዋ 5፥11፤ 20፥28 ኤፌ 5፥23-33።
ሥርዓተ አምልኮ የተጀመረው እግዚአብሔር ፍጥረቱን እመ ኁበ አልቦ ኁበ ቦ አምጥቶ ከፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ነው። መላእክት ከተፈጠሩበት ጊዜ ጀምሮ ”ቅዱስ፣ቅዱስ፣ቅዱስ” እያሉ ፈጣሪያቸውን በማመስገን አምልኮአቸውን የሚገልጹ ስለሆነ አምልኮተ እግዚአብሔር በዓለመ መላእክት ተጀመረ ማለት ነው /ኩፋ 2፥6 8።
ሰውም በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ለፈጣሪው ይገዛ ነበር። ልጆችም ከአባታቸው ባገኙት መንፈሳዊ ጥበብ መሠረት የአምልኮአቸው መገለጫ የሆነ መሥዋዕት የወንጌል አምሳልና መርገፍ በሆነችው ኦሪት አቅርበዋል።አማናዊት ቤተክርስቲያን የተመሠረተችው ግንቦት 18 ቀን 33 ዓ.ም እንደሆነ ተጽፏል።
በክርስቶስ ደም የተመሠረተችው አንዲት፣ቅድስት፣ኩላዊት፣ሐዋርያዊት ቤ/ያናችን በአሁኑ ሰዓት በመላው ዓለም ማለትም በአፍሪካ በአሜሪካ፣በካናዳ፣ኢንግላንድን ጨምሮ በመላው አውሮፓ፣ በእስያ ና በኢየሩሳሌም የምትታወቅ እና ተቀባይነት ያላት ሲሆን ፤ በዚህ በውጭው ዓለም ለሚገኘው ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ እና ለሌላውም ፣ማኅበረሰብ በስደት ምክንያት ባህሉ ን፣ታሪኲንና ማንነቱን እንዳይረሳ ፣ከሃይማኖቱ እንዳወጣ ለማድለግ ፦ ጳጳሳትን ፣ካህናትን ፣ዲያቆናትን ና መምህራንን ልካ ፦ ሃይማኖታዊ፣ማኅበራዊ፣መንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ሐዋርያዊ ተልዕኮዋን በመወጣት ላይ ትገኛለች።
በዚሁ መሠርት በኖርዌይ ስታቫንገር የኢ/ኦ/ተ/ ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ወኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ታላቁ አባት ብጹዕ አቡነ ጎርጎሪዎስ ካልዕ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክንን በዓለም መድረክ ወክለው ከላይ ለተገለጸዉ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸው ወደ ኖርዌይ ስታቫንገር መምጣታቸውን ተከትሎ እ. ኤ. አ 1994 ዓ.ም በፈቃደ እግዚአብሔር ልትመሠረት ችላለች ።
ብጹዕ አቡነ ጎርጎሪዎስ ካልዕ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክንን ታላቅነትና ማንነት በዓለም ያሳወቁ የቤ/ክ ልዩ መልዕክተኛ ነበሩ። ብጹዕ አባታችን ከአምስት በላይ የተለያዩ ቋንቋዎች ተሰጥኦና ልዩ ልዩ የንግግር ጸጋ፣ ሰብኮ የማሳመንና ተናግሮ የማሳሰብ ሃብት ስለነበራቸው ቅዱስ ሲኖዶስ በየጊዜው በተለያዩ ዓለም አቀፋዊ ጉባኤዎች የኢትዮጵያን ቤ/ክ ወክለው እንዲገኙ በወሰነው መሰረት፦ በተለያዩ የዓለም ሀገራት በተካሄዱ ስብሰባዎች ለይ ተገኝተዋል።በዚህም መሠረት በአውሮፓ በነበራቸው አገልግሎት በኖርዌይ ስታቫንገር ከተማ ይኖሩ ከነበሩት በጣት ከሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ ምእመናን መካከል ወ/ሮ ኂሩት ከበደ እና ቤተሰቦቻቸውን አግኝተው አስተምረው፣ መክረውና አባታዊ ቡራኬ ከሰጧቸው በኃላ ቤተክርስቲያን እንዲመሠርቱ በሰጧቸው አባታዊ ማሳሰቢያ መሠረት ምእመናኑን በማሰባሰብ አገልግሎት በ20.07.1994 ዓ.ም (እ. ኤ. አ) ተጀመረ።
በ06.04.2005 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ቤተክርስቲኗ በኖርዌይ ሀገር ሕጋዊ ሆና ተመዘገበች።በአሁኑ ሰዓት የምእመናን ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ለማነጽ ወይም ለመግዛት ምእመናን በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ።
እንኳን ለዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት (ኒቆዲሞስ) በሰላም አደረሳችሁ!
የአይሁድ አለቃ፣ የእስራኤል መምህር ኒቆዲሞስ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃለ ምልልስ ካስተማራቸው ጥቂት ዕድለኛ ሰዎች አንዱ ነው፡፡ «ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ ስለ መወለድ» ዮሐ. ፫፥፮ ጌታችን ኒቆዲሞስን በምሳሌ አድርጎ ያስተማረው ሲሆን ሌሊት ከአምላኩ ተምሮ ምሥጢሩ የተገለጸለት ኒቆዲሞስ ቀድሞ በአደባባይ ሄዶ መማርን ቢፈራም ምሥጢሩ ሲገለጽለት ግን አይሁድ ጌታችንን በሰቀሉት ዕለት ፍርኃት ርቆለት ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ቅዱስ […]
እንኳን ለደብረ ዘይት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
“እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽእ፤ ወአምላክነሂ ኢያረምም፤ እሳት ይነድድ ቅድሜሁ፡፡” እግዚአብሐር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳቱ በፊቱ ይቃጠላል፡፡ መዝ.፵፱፥፪-፫
እንኳን ለደብረ ዘይት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኖርዌይ የስታቫንገር ደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ወኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአገ ገነት መምህር የኔታ አብርሃም ሙጭየ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት።
እንኳን ለዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ለምኵራብ) በሰላም አደረሳችሁ!
“ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ትሰመይ”(“ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላላች” ማቴ.21÷13)
ምኵራብ ማለት:- የአይሁድ መሰብሰቢያ አዳራሽ ፣ ቤተ መቅደስ ፣ ኮረፍታ ማለት ነው
በዚህ ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቤተ መቅደሱን ክብር የገለጠበት በአንጻሩ ለቤተ መቅደሱ ክብር ሳይሰጡ በቤተ መቅደሱ የማይገባ ስራ የሚሰሩትን የገሠጸበትና ያስተማረበት ነው።
የእናታችን የቅድስት ኪዳነ ምሕረት የንግሥ በዓል በደብረ ገነት መድኃኔዓለም ወኪዳነምሕረት ቤተ ክርስቲያን በመዝሙር በትምህርተ ወንጌል በማህሌት እና በቅዳሴ ከየካቲት 14 -15, 2018 ዓም (Feb 21-22, 2026) ብፁዕ አባታችን አቡነ ኤልያስ በተገኙበት በድምቀት ተከበረ።
“ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ” «ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ» መዝ. 88 (89) ፥ 3 የደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የየካቲት ኪዳነ ምሕረትን ዓመታዊ ክብረ በዓል በጥቂቱ፦
“ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ ወታጸምም ኵሎ ፍትወታተ ዘሥጋ”(ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች የሥጋን አላስፈላጊ ፍላጎቶችንም ታስወግዳለች) ቅ.ያሬድ
እንኳን ለዐቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ! ዐቢይ ጾም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀደመው ዘመን ለነበሩት አባቶችና እናቶች ጾም ጠቃሚና አስፈላጊ እንደሆነ በነቢያቱ አድሮ ያስተማረ እርሱ በሥጋ ማርያም ተገልጦ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ፵ (40) መዓልት ፵ (40) ሌሊት የጾመው ታላቅ ጾም ነወ። እርሱ ጾሞ ፈተናዎችን ድል ነስቶ እናንተም ጾማችሁ ፈተናዎችን ድል ንሡ ሲለን ነው። ዐቢይ ጾም ከ፯ቱ አጽዋማት […]
እንኳን ለዘመነ ቅበላ(ዘመነ መርዓዊ ወመርዓት) በሰላም አደረሳችሁ!
እንኳን ለዘመነ ቅበላ(ዘመነ መርዓዊ ወመርዓት) በሰላም አደረሳችሁ!
ከነነዌ ፋሲካ ሐሙስ ጀምሮ እስከ ዘወረደ ዋይዜማ ቅዳሜ ድረስ ያለው ዘመን ዘመነ ቅበላ (ዘመነ መርዓዊ ወመርዓት) ይባላል።
እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!
እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!
ጾመ ነነዌ ከሰባቱ የህግ(የቀኖና) አጽዋማት አንዷ ናት ከጥር17 ቀን እስከ የካቲት 21 ቀን ድረስ ባሉት 35 ቀናት ውስጥ ብቻ ትውላለች ከታች ጥር 16 ቀንን ከላይ የካቲት 22 ቀንን አትነካም ዘንድሮ በ2018 ዓ.ም ከጥር 25 እስከ ጥር 27 ቀን ድረስ ትውላች።
አስተርእዮ ማርያም
አስተርእዮ ማርያም
ጥር ፳፩ ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው። እመ ብዙኃን ቅድስት ድንግል
እንኳን ለዘመነ አስተርእዮ በሰላም አደረሳችሁ!
እንኳን ለዘመነ አስተርእዮ በሰላም አደረሳችሁ!
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ መሠረት ከጥር ፲፩(11) እስከ ድኅራረ ጾም ቅዳሜ ደረስ ያለው ዘመን ዘመነ አስተርእዮ ይባላል።( ዘመነ አስተርእዮ ሲበዛ ፶፫(53) ቀን ይሆናል ከጥር ፲፩ (11) እስከ መጋቢት ፫(3) ድረስ ማለት ነው ፤ ሲያጥር ፲፱(19) ቀን ይሆናል ከጥር ፲፩(11) እስከ ጥር ፳፱(29) ቀን ድረስ ማለት ነው።ከእነዚህ ቀናት መካከል አይወጣም።