አስተርእዮ ማርያም

አስተርእዮ ማርያም

ጥር ፳፩ ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው። እመ ብዙኃን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕረፍቷ በዘመነ አስተርእዮ ማለትም የልጇ የወዳጇ የአምላኳ፤ የአምላካችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁም የቅድስት ሥላሴ መገለጥ በሆነበት ወቅት በመዋሉ አስተርእዮ ማርያም ይባላል። እመቤታችን ከቅድስት ሐና እና ከቅዱስ ኢያቄም ጋር ፫ ዓመታትን፣ በቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመታትን፣ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ፴፫ ዓመታት ከሦስት ወራትን፣ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ፲፭ ዓመታትን፣ በአጠቃላይ ፷፬ ዓመታትን በዚህ ዓለም ኖራ በ፵፱ ዓ.ም በክብር ዐርፋለች፡፡ በዕለቱ ጥር  ፳፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ከደረሱት የስብሐተ ነግህ፣ የኪዳን እና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በከፊል:-

የደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ስታቫንጋር ኖርዌይ