እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!

እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!
ጾመ ነነዌ ከሰባቱ የህግ(የቀኖና) አጽዋማት አንዷ ናት ከጥር17 ቀን እስከ የካቲት 21 ቀን ድረስ ባሉት 35 ቀናት ውስጥ ብቻ ትውላለች ከታች ጥር 16 ቀንን ከላይ የካቲት 22 ቀንን አትነካም ዘንድሮ በ2018 ዓ.ም ከጥር 25 እስከ ጥር 27 ቀን ድረስ ትውላች።
‹‹የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፤ ከታላቁ ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ›› ትን.ዮና. ፫÷፭-፮
እግዚአብሔር የነነዌ ሰዎችን ያዘነላቸው ስለ ኃጢአታቸው አዝነው በመገኘታቸውና ጾም እና ጸሎትን በመያዛቸው ነው። የእግዚአብሔርን ርኅራኄ፣ የነቢዩ የዮናስን የዋህነትና የሕዝቡን የንሥሐ፣ የጾምና የጸሎት ሕይወት እንማርበታለን።
በዕለተ በእሑድ ጥር ፳ ፬(24) ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ (2018) ዓ. ም (February 1/2026) ከደረሱት የስብሐት ነግህ ፤ የኪዳን ፤ የቅዳሴ ፤ የስብከተ ወንጌልና የዝማሬ አግልግሎት መካከል በትንሹ(በከፊል)፦
በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት የደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ስታቫንጋር፣ ኖርዌይ