“ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ ወታጸምም ኵሎ ፍትወታተ ዘሥጋ”(ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች የሥጋን አላስፈላጊ ፍላጎቶችንም ታስወግዳለች) ቅ.ያሬድ
እንኳን ለዐቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ!
ዐቢይ ጾም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀደመው ዘመን ለነበሩት አባቶችና እናቶች ጾም ጠቃሚና አስፈላጊ እንደሆነ በነቢያቱ አድሮ ያስተማረ እርሱ በሥጋ ማርያም ተገልጦ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ፵ (40) መዓልት ፵ (40) ሌሊት የጾመው ታላቅ ጾም ነወ።
እርሱ ጾሞ ፈተናዎችን ድል ነስቶ እናንተም ጾማችሁ ፈተናዎችን ድል ንሡ ሲለን ነው።
ዐቢይ ጾም ከ፯ቱ አጽዋማት አንዱ ሲሆን የየራሳቸው ስያሜ ያላችው ፰(8) ሳምንታት ወይም ፶ ፭ (55) ቀናት አሉት።ከእነዚህም ውስጥ ፰(8) ቅዳሜ ፯(7) እሑድ አሉ እነዚህን ከቁጥር ባያስገቡ ፵(40) ቀናት ይሆናል።
የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ ይባላል።
ዘወረደ ጌታችን፣ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት መውረዱን፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን፣ የእኛን ሥጋ መዋህዱን ሰው ኾኖ መገለጡን ይታሰብበታል።
በተጨማሪ ይህ ሳምንት ጾመ ሕርቃል፣ ጾመ ሙሴ ተብሎም ይጠራል።
የዘወረደ በዕለተ በእሑድ የካቲት ፰(8) ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ (2018) ዓ. ም (February 15/2026) ከከደረሱት የስብሐት ነግህ ፤ የኪዳን ፤ የቅዳሴ ፤ የስብከተ ወንጌልና የዝማሬ አግልግሎት መካከል በትንሹ(በከፊል)፦

